ዜና

የሀገር ውስጥ ዜና

የተረጋጋ ሀገር እንዲኖር በትምህርት ዘርፉ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነትን እያረጋገጡ መሄድ ያስፈልጋል፤ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዳሰነች ወረዳ የተገነባውን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት በትምህርት አቅርቦት ረገድ በሁሉም አካባቢ ምንም ልዩነት ሊፈጠር አይገባም ብለዋል።
ይህንንም ለማረጋገጥም በትምህርት ዘርፉ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት ተቀርፀው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝም አብራርተዋል ።
በተለይም ምቹ የመማሪያ ከባቢን በሁሉም አካባቢ ለመፍጠር “በትምህርት ለትውልድ” የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል ንቅናቄ በርካታ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንና የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገና መደረጉን አንስተዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ መሆኑን በማመን በከተማና በባለሀብቶች ብቻ ታጥሮ የቆየውን የቅድመ አንደኛ ትምህርት በመቀየር በሁሉም አካባቢ ያለ ልዩነት ትኩረት ተሰጥቶ መሠራቱን ጠቅሰዋል።
በዚህም ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በከተማና በገጠር ተገንብተው የአምስተና ስድስት ዓመት ህፃናት እየተማሩ እንደሚገኙ አብራርተዋል።
ትምህርት ለሁሉ ነገር ወሳኝ በመሆኑ ልጆቻችንን በአግባቡ በማስተማር የአለምን ፈተና መቋቋም የሚችሉ ጠንካራ ሀገር ተረካቢዎችን ለመፍጠር መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።
አክለውም የትምህርት ሥራ ከፖለቲካ መላቀቅ አለበት ያሉት ሚኒስትሩ ሁሉም ነገር ፖለቲካ መሆኑ ቀርቶ ትምህርት የሁላችን እንዲሆን በማድረግ ለዜጎች ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል በመስጠት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ይገባናል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።
Mar 01, 2026 225
የሀገር ውስጥ ዜና

በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች እኩል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ አሞራቴ ከተማ የተገነባው የአሞራቴ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመርቋል፤ ተጨማሪ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት እቅድ ተይዟል።
በትምህርት ሚኒስቴርና በሰዎች ለሰዎች ግብረ ሰናይ ድርጅት የተገነባውን ትምህርት ቤት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ መርቀውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት መልዕክት በትምህርት ዘርፉ ሁሉም ዜጎች አኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ ለማስቻል ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።
ይህ ዛሬ በዳሰነች የተመረቀው አዳሪ ትምህርት ቤት አርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የራሱን ሥራ ሲሰራ ልጆቹ ተረጋግተው የሚማሩበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል።
እነሱን ሳናስተምር ይች ሀገር ለሁላችንም እኩል ነች ማለት ከባድ ነው ያሉት ሚኒስትሩ የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ትልቅ ደስታን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
በቀጣይ ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሌላቸው ወረዳዎችን በመለየት 1452 ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት እየተሰራ ሲሆን በዳሰነችም ሁለት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይገነባል ብለዋል።
መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ከአምስት ዓመት ጀምሮ ለማስተማር በሰጠው ልዩ ትኩረት ባለፉት ዓመታት ከ34ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውንም ጠቅሰዋል።
ይች ሀገር የተወሰኑ ሰዎች ሀገር ሳትሆን የሁሉም የኢትዮጵያውያን በመሆኗ የተረጋጋ ሀገር እንዲኖረን በትምህርት ዘርፉ ያለልዩነት እኩል ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ ይገባልም ብለዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው መንግስት በትምህርት ዘርፉ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስተካከል ባለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት በተሰራው ስራ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ገልፀዋል።
ይህ ትምህርት ቤት ለዚህ አካባቢ ትርጉሙ ትልቅ ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተሻለ ነገ እንዲኖር ዛሬ የተሻለ ነገር እየሰራ ላለው ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋና አቅርበዋል ።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ሰባስቲያን ብራዲስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች ከዚህ ቀደም በገነባቸው ትምህርት ቤቶች በርካታ ሙሁራን መውጣታቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ ትምህርት ቤትም ነገ ሀገር መምራት የሚችሉ ልጆች እንደሚወጡ ያላቸውን እምነት ገልፀው ትምህርት ቤቱ ዘላቂነት እንዲኖረው በባለቤትነት መንከባከብ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
Feb 28, 2026 205
የሀገር ውስጥ ዜና

የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ትምህርት ሚኒስቴር ከሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ያስገነባው የአማሮ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በዛሬው እለት ተመርቋል።
ትምህርት ቤቱን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተገኝተው መርቀውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ዛሬ የተመረቀው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደ ሀገር ትምህርትን በፍትሃዊነት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ማሳያ ነው ብለዋል።
ከለውጡ ወዲህ እንደ በፊቱ የመሠረት ድጋይ አስቀምጦ መሄድ ቀርቷል ያሉ ሲሆን በትምህርት ሴክተሩ ፕሮጀክት ጀምሮ በአጠረ ጊዜ መጨረስ ባህል እየሆነ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
የትምህርት ሴክተሩ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ ወድቆ በመቆየቱ ከዚህ ለማላቀቅ የተለያዩ የሪፎርም ተግባራት እየተተገበሩ መሆኑንና በተለይም ኩረጃን የሚጠየፍ በራሱ መስራትና መተማመን የሚችል ትውልድ ለመፍጠር እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
አክለውም የትምህርት ስራ የሚለወጠው ከታች ጀምሮ ሲሰራ በመሆኑ በሁሉም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲኖሩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም ባለፉት አመታት ከ34ሺ በላይ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ጠቅሰው በቀጣይ 1452 ትምህርት ቤቶች በ726 ወረዳዎች በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሎች ትብብር እንደሚገነቡ ጠቁመዋል ።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸው ትምህርት ለሁለንተናዊ እድገትና ለዜጎች ከፍ ማለት ወሳኝ መሣሪያ በመሆኑ መንግስት በሪፎርሙ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
የትምህርት ሴክተሩ እጅግ ስኬታማ ከሆኑ ተቋማት ውስጥ የሚጠቀስ መሆኑን አንስተው በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተገኘው ውጤት የሚደነቅ ነውም ብለዋል።
ይህ ትምህርት ቤትም ስታንዳርዱን ጠብቆ የተገነባ በመሆኑ ህብረተሰቡ በባለቤትነት ጠብቆ በመከባከብ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ሰባስቲያን ብራንስ በበኩላቸው ሰዎች ለሰዎች በትምህርት፣በጤና፣ በምግብ ዋስተናና በውሃ አቅርቦት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
የዚህ ትምህርት ቤት መገንባት ሰፊ እድል ይዞ የመጣ በመሆኑ ውጤታማ ለመሆን ተማሪዎች ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።
Feb 27, 2026 185
የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች 130ኛውን የአድዋ ድል በዓልን '' አድዋ 130፣ ከአኩሪ ታሪክ፣ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል አገራዊ መሪ ቃል አክብረዋል።
‎የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አድዋ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለመላው ጥቁር ህዝቦች ነጻነት ህያው ተምሳሌት በመሆኑ አባቶቻችንና እናቶቻችን በከፈሉት መስዋዕትነትና ላጎናጸፉን ድል ክብር ይገባቸዋል ብለዋል።
‎ትምህርት ለምናደርገው የእድገትና የብልጽግና ጉዞ ቁልፍ ሚና ያለው በመሆኑ ጅምር ስራዎቻችንን አልቆ በመፈጸም እንደሚገባ ክብርት ሚኒስትር ደኤታ አስገንዝበዋል።
‎አገራችን ለዜጎቿ የተመቸችና የልማት ተምሳሌት ወደምትሆንበት ደረጃ ለመውሰድ የትምህርት ዘርፉ ተዋናዮች የበኩላቸውን ድርሻ በላቀ የአገር ፍቅርና ስሜት መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ክብርት ወ/ሮ አየለች አንስተዋል።
‎የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ከመሠረቱ በህጻናት ላይ መስራት የሚገባን መሆኑን በመረዳት ለህጻት ትምህርት የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።
‎ዳር ድንበሮቻችንን ለመጠበቅና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ለማዝለቅ አንድነታችንን ማጠናከር እንደሚገባም ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል።
‎የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበኩላቸው ለአንድነታችንና ለብሔራዊ ጥቅማችን ባለው ፋይዳ ላይ ግንዛቤ መፍጠር የክብረ በዓሉ ዓላማ መሆኑን አስተው አድዋ በዓለም ታሪክ አፍሪካዊት አገር ቅኝ ግዛትን በጦር ኃይል ያሸነፈችበትና በደማቅ ቀለም የተጻፈ ታሪካዊ ተምሳሌት የሆነችበት አኩሪ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ የውይይት መነሻ ጽሁፍ ያቀረቡት የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ይማም በበኩላቸው የአድዋ ድል ብሔራዊ የአንድነትና የአሸናፊነት ምልክት መሆኑን አስረድተዋል።
‎የብሄራዊ ጥቅም የመጀመሪያው መነሻ ሉዓላዊነት በመሆኑ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ ዜጎች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባም ገልጸዋል።
‎በክብረ በዓሉ ላይ በተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
Feb 27, 2026 172
የሀገር ውስጥ ዜና

እንደ ሀገር የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ባልሆነባቸው ወረዳዎች ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የትምህርት ቤት ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል።

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን መሰረተ ልማት ለሟሟላትና ለማሻሻል በቀረጸው የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ በርካታ ትምህርት ቤቶች ተገንብተዋል።
በተለይም ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት በመስጠት እና በትምህርትና ስልጠና ፖሊሲው ነጻና የግዴታ ትምህርት እንዲሆን በማመላከት ከ34000 በላይ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛል።
ባለፉት ዓመታት እነዚህ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም የነበረውን ክፍተት በሚፈለገው ልክ መሙላት ባለመቻሉ በርካታ ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል፤ ይንንም ለመቅረፍና ተደራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።
በዚህም ‎ትምህርት ቤቶቹን ለመገንባት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ተደራሽ ያልሆነባቸው አካባቢዎችና የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወረዳዎች ልየታ መደረጉም ተገልጿል።
በነዚህ በተለዩ ወረዳዎች ለትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ትምህርት ሚኒስቴር በውጤት ተኮር የገንዘብ ድጋፍ ስርዓት ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ ግንባታውን ለማከናወን አቅዶ እየሰራ መሆኑም ተመላክቷል።
ከሚገነቡት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የዋጋ ጥናት 726ቱ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነቡ ይሆናል። እነዚህ የትምህርት ተቋማት የሚገነቡት ክልሉ በተጠቀሱት ወረዳዎች ወይም አካባቢዎች ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰራው ልክ በክልሉ በጀት ወይንም ከማህበረሰቡ አሰባስቦ መገንባት የሚችል ከሆነ ብቻ ነው።
በዚህም በቀጣይ 6 ወራት ትምህርት ሚኒስቴር 726 እንዲሁም ክልሎች በተመሳሳይ 726 በአጠቃላይ 1452 የሚደርሱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመላ ሀገሪቱ ለመገንባት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የትምህርት ቤቶቹ ግንባታ ዲዛይን የተሰራ ሲሆን እንደየ አካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ መጠነኛ ለውጥ እንዲኖራቸው እንደሚደረግና ቢያንስ ሁለት የመማሪያ ፣ የመመገቢያ ፣ የህጻናት ማረፊያ ፣ የመምህራን ቢሮ፣ የመጸዳጃ ክፍሎችና ህጻናትን ለፈጠራ በማነሳሳት ሁለንተናዊ እድገታቸው ላይ አወንታዊ ሚና የሚጫወቱባቸው የመጫወቻ ቦታዎች እንደሚኖራቸው ተደርጎ መዘጋጀቱም ተጠቁሟል።
‎የእነዚህ ትምህርት ቤቶቹ መገንባት ሁሉም የኢትዮጵያ ህጻናት አንደኛ ክፍል ከመግባታቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ዓመት የቅድመ አንደኛ ደረጃ የዝግጁነት ትምህርት እንዲያገኙ የሚያስችላቸውም ይሆናል።
Feb 23, 2026 168
የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ለአይነ ስውራን የተዘጋጁ የ2ኛ ደረጃ የብሬል መጽሐፍት እየተጓጓዙ ነው።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በመጀመሪያው ዙር ለስርጭት የተዘጋጁ የብሬል መጽሀፍቱን የስርጭት ሂደት ተመልክተዋል።
‎ክብርት ሚኒስትር ዴኤታዋ የመጽሐፍቱን ስርጭት ሂደት ምልከታ ባደረጉበት ወቅት እንደገለጹት የትምህርት ጥራት፣አግባብነት ፣ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋጥ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ ይገኛል ብለዋል።
‎ከሪፎርም ስራዎች መካከልም የተሻሻለውን የትምህርትና ስልጠና ፖሊሲ መነሻ በማድረግ አዲስ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ተግባራዊ መደረጉን ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ገልጸዋል።
‎ተግባራዊ በተደረገው ሥርዓተ ትምህርት መሠረትም ተማሪዎችና መምህራን የሚገለገሉባቸውን የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሀፍት አንድ ለአንድ ለማድረስ ሲሰራ መቆየቱንም ክብርት ወ/ሮ አየለች ተናግረዋል።
‎ሁሉም ዜጎች የመማርና የመማሪያ ግብዓቶችን ማግኘት መብት እንዳላቸው ያስገነዘቡት ክብርት ሚኒስትር ዴኤታ ዜጎች በሁሉም ረገድ እኩል የትምህርት እድል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
‎ለስርጭት የተዘጋጁት የብሬል መጽሐፍት አይስውራን ተማሪዎች በቂ የመማሪያ መጽሐፍት አግኝተው ራሳቸውን በማብቃት ከሌሎች ተማሪዎች ጋር እኩል እድል እንዲያገኙና በእውቀትና በክህሎት ብቁ ሆነው እንዲገኙ እንደሚያስችሉ ገልጸዋል።
‎የቅድመ አንደኛና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከ 23.9 ሚሊዮን በላይ መጽሐፍት ታትመው እየተሰራጩና እየተጓጓዙ እንደሚገኙም ጠቁመዋል።
‎የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ በበኩላቸው በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ሂደት ለስርጭት የተዘጋጁት የ2ኛ ደረጃ የብሬል መማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት በስድስት (6) የትምህርት ዓይነቶች የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
‎የብሬል መጽሀፍቱ ለሁሉም ክልል አይነ ስውራን ተማሪዎች መታተማቸውን የገለጹት ወ/ሮ ዛፉ በአሁኑ ወቅት ታትመው የተጠናቀቁት የብሬል መጽሐፍት ከማዕከል ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ከሰኞ ጀምሮ እንደሚጓጓዙ ጠቁመዋል።
Feb 16, 2026 161
የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች ኃላፊነታቸውን በትክክል እንዲወጡ ተጠየቀ ።

በቅርቡ አዲስ የተመደቡ የቦርድ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተረድተው ወደ ተግባር እንዲገቡ የሚያስችል የሥራ ትውውቅና መመሪያ ተሰጥቷል።
በመድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ ባስተላለፉት መልዕክት አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች የተጣለባቸውን አገራዊ አደራ ለመወጣት የተመደቡበት ተቋም ተልዕኮና የሥራ ድርሻ በውል መረዳት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም አመራሩ የተሰጠውን የሥራ ኃላፊነት በጥልቀት አውቆና ተረድቶ መስራቱ ለተቋሙ ስኬት መሰረታዊ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የምርምር ማዕከል በመሆናቸው አመራሩ ግልጽ ራዕይ ይዞ መንቀሳቀሱ የተቋማዊ ለውጥ (Reform) ስራዎችን በብቃት ለመምራትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርምና መደበኛ ስራዎችን አስመልክቶ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።
አዳዲሶቹ አመራሮች የተሰጣቸውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ወደ ስራ ሲሰማሩ የተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ ካለው ሀገራዊ የሪፎርም አቅጣጫ ጋር በማጣጣም መከወን እንደሚገባቸውም አቅጣጫ ተቀምጧል።
በቅርቡ አዲስ የተመደቡ የቦርድ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ተረድተው ወደ ተግባር እንዲገቡ የሚያስችል የሥራ ትውውቅና መመሪያ ተሰጥቷል።
በመድረኩ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ ባስተላለፉት መልዕክት አዲስ የተመደቡ የዩኒቨርስቲ አመራሮች የተጣለባቸውን አገራዊ አደራ ለመወጣት የተመደቡበት ተቋም ተልዕኮና የሥራ ድርሻ በውል መረዳት እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም አመራሩ የተሰጠውን የሥራ ኃላፊነት በጥልቀት አውቆና ተረድቶ መስራቱ ለተቋሙ ስኬት መሰረታዊ ፋይዳ እንዳለው አስገንዝበዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የምርምር ማዕከል በመሆናቸው አመራሩ ግልጽ ራዕይ ይዞ መንቀሳቀሱ የተቋማዊ ለውጥ (Reform) ስራዎችን በብቃት ለመምራትና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።
በመድረኩ ላይ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በመከናወን ላይ ያሉ የሪፎርምና መደበኛ ስራዎችን አስመልክቶ ሰፊ ገለጻ ተደርጓል።
አዳዲሶቹ አመራሮች የተሰጣቸውን መመሪያ መሰረት በማድረግ ወደ ስራ ሲሰማሩ የተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ ካለው ሀገራዊ የሪፎርም አቅጣጫ ጋር በማጣጣም መከወን እንደሚገባቸውም አቅጣጫ ተቀምጧል።
Feb 13, 2026 91
የሀገር ውስጥ ዜና

ትምህርት ሚኒስቴር ያሳተማቸው የቅድመ አንደኛ እና የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍት ከጅቡቲ ወደ ሀገር ውስጥ መግባት መጀመራቸው ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ባገኘው ድጋፍ ያሳተማቸው የቅድመ አንደኛ እና የአንደኛ ደረጃ መጽሃፍት በገላን የመጽሃፍት ክዘና ማዕከል እየተራገፉ ይገኛል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከአጋር አካላት ባገኘው ድጋፍ ከ23.9 ሚሊየን በላይ መጽሃፍትን በማሳተም ከጅቡቲ ወደ ሃገር ውስጥ ማጓጓዝ መጀመሩን የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ ገልጸዋል።
በዚህም ከ30 ኮንቴነር በላይ መጽሃፍት በገላን የክዘና ማዕከል መድረሳቸውን የገለጹት ሥራ አስተፈጻሚዋ አሁን የደረሱትን መጽሐፍት ክልሎች እንዲረከቡ ከስር ከስር የማሰራጨት ሥራ ይሰራል ብለዋል። በትክክል ለተማሪዎች መሰራጨታቸውን የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
መጽሐፍቶቹም ሲታተሙ በሁሉም ክልል እና ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ዞኖች የሚያሳይ መለያ ኪውአር ኮድ (QR CODE) የተካተተ በመሆኑ የሁሉንም ዞኖች መጽሐፍቶች በመለያ ኮዳቸው መከታተል የሚቻልበት አሰራር መኖሩንም አብራርተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ያደረሰ ሲሆን የቅድመ አንደኛ እና የአንደኛ ደረጃ መጽሃፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ እንዲቻል ለክልሎች ድጋፍ በማድረግ ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ባገኘው ድጋፍ ያሳተማቸው የቅድመ አንደኛ እና የአንደኛ ደረጃ መጽሃፍት በገላን የመጽሃፍት ክዘና ማዕከል እየተራገፉ ይገኛል።
የትምህርት ሚኒስቴር የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ ከአጋር አካላት ባገኘው ድጋፍ ከ23.9 ሚሊየን በላይ መጽሃፍትን በማሳተም ከጅቡቲ ወደ ሃገር ውስጥ ማጓጓዝ መጀመሩን የሥርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ዛፉ አብርሃ ገልጸዋል።
በዚህም ከ30 ኮንቴነር በላይ መጽሃፍት በገላን የክዘና ማዕከል መድረሳቸውን የገለጹት ሥራ አስተፈጻሚዋ አሁን የደረሱትን መጽሐፍት ክልሎች እንዲረከቡ ከስር ከስር የማሰራጨት ሥራ ይሰራል ብለዋል። በትክክል ለተማሪዎች መሰራጨታቸውን የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
መጽሐፍቶቹም ሲታተሙ በሁሉም ክልል እና ከተማ አስተዳደር የሚገኙ ዞኖች የሚያሳይ መለያ ኪውአር ኮድ (QR CODE) የተካተተ በመሆኑ የሁሉንም ዞኖች መጽሐፍቶች በመለያ ኮዳቸው መከታተል የሚቻልበት አሰራር መኖሩንም አብራርተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መጽሐፍትን አንድ ለአንድ ያደረሰ ሲሆን የቅድመ አንደኛ እና የአንደኛ ደረጃ መጽሃፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ እንዲቻል ለክልሎች ድጋፍ በማድረግ ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
Feb 12, 2026 84
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተማሪ መጽሃፍትን አንድ ለአንድ ለማድረስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፤

ትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት በተገኘ ድጋፍ ያሳተማቸውን 23.9 ሚሊየን የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍት ጅቡቲ ወደብ ደርሰው ወደ ሃገር ውስጥ የማጓጓዝ ሥራ እየተሰራ ነው።
ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የተማሪ መጽሃፍትን በሁሉም የትምህርት እርከኖች አንድ ለአንድ ለማድረስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን ማሟላት የክልል ትምህርት ቢሮዎች ሃላፊነት መሆኑን ያነሱት የትምህርት ሚኒስትሩ ነገር ግን እንደ ሀገር የሚታየውን የተማሪ መጽሃፍት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በትምህርት ሚኒስቴር ደረጃ ሀብት በማፈላለግ ከ23.9 ሚሊየን በላይ መጽሃፍትን ማሳተም መቻሉን አብራርተዋል።
እነዚህ የታተሙት መጽሃፍት ጅቡቲ ወደብ ደርሰው የተወሰኑት ወደ ሀገር ውስጥ መግባት መጀመራቸውን ጠቅሰው በመጪዎቹ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ ሀገር ውስጥ ተጠናቀው በመግባት ለሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በተቀናጀ ሁኔታ የሚሰራጩ በመሆኑ ክልሎች በፍጥነት በመረከብ ወደ ትምህርት ቤት በማውረድ ተማሪዎቹ መጽሃፍቱን እንዲያገኙ በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በክልሎችና በትምህርት ሚኒስቴር የታተሙት መጽሃፍት በቂ አለመሆናቸውን የገልጹት ሚኒስትሩ በቀጣይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽህፍትን አንድ ለአንድ ለማደረስ ትምህርት ሚኒስቴር ከተባባሪ አካላት ባገኘው ድጋፍ ተጨማሪ ወደ 40 ሚሊየን የሚጠጋ መጽሃፍትን በድጋሚ አሳትሞ ለክልሎች ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን አሳትሞ ሙሉ በሙሉ ለተማሪዎች አንድ ለአንድ እንዲደርስ ወደ ክልሎች ማሰራጨቱ የሚታወስ ነው።
ትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር አካላት በተገኘ ድጋፍ ያሳተማቸውን 23.9 ሚሊየን የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍት ጅቡቲ ወደብ ደርሰው ወደ ሃገር ውስጥ የማጓጓዝ ሥራ እየተሰራ ነው።
ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የተማሪ መጽሃፍትን በሁሉም የትምህርት እርከኖች አንድ ለአንድ ለማድረስ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን ማሟላት የክልል ትምህርት ቢሮዎች ሃላፊነት መሆኑን ያነሱት የትምህርት ሚኒስትሩ ነገር ግን እንደ ሀገር የሚታየውን የተማሪ መጽሃፍት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በትምህርት ሚኒስቴር ደረጃ ሀብት በማፈላለግ ከ23.9 ሚሊየን በላይ መጽሃፍትን ማሳተም መቻሉን አብራርተዋል።
እነዚህ የታተሙት መጽሃፍት ጅቡቲ ወደብ ደርሰው የተወሰኑት ወደ ሀገር ውስጥ መግባት መጀመራቸውን ጠቅሰው በመጪዎቹ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ ሀገር ውስጥ ተጠናቀው በመግባት ለሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በተቀናጀ ሁኔታ የሚሰራጩ በመሆኑ ክልሎች በፍጥነት በመረከብ ወደ ትምህርት ቤት በማውረድ ተማሪዎቹ መጽሃፍቱን እንዲያገኙ በማድረግ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል።
እስካሁን በክልሎችና በትምህርት ሚኒስቴር የታተሙት መጽሃፍት በቂ አለመሆናቸውን የገልጹት ሚኒስትሩ በቀጣይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መጽህፍትን አንድ ለአንድ ለማደረስ ትምህርት ሚኒስቴር ከተባባሪ አካላት ባገኘው ድጋፍ ተጨማሪ ወደ 40 ሚሊየን የሚጠጋ መጽሃፍትን በድጋሚ አሳትሞ ለክልሎች ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መጽሃፍትን አሳትሞ ሙሉ በሙሉ ለተማሪዎች አንድ ለአንድ እንዲደርስ ወደ ክልሎች ማሰራጨቱ የሚታወስ ነው።
Feb 10, 2026 432
የሀገር ውስጥ ዜና

መጪዎቹ ስድስት ወራት ከ1200 በላይ የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመገንባት መታቀዱ ተገለፀ። እነዚህ ትምህርት ቤቶች እንደ ሀገር ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው ወረዳዎችን የሚገነቡ ናቸው።

የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀሪ ስድስት ወራት የሚከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ለክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሀላፊዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች ባገኘው ድጋፍ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙና ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው 626 ወረዳዎች ውስጥ አንድ አንድ ትምህርት ቤት የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክትም ተጠቃሚ የሚሆኑ ክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የትምህርት ሚኒስቴር ባገኘው ድጋፍ በየወረዳው በሚገነባው ትምህርት ቤት ተመሳሳይ ሌላ ት/ቤት እንዲገነቡ የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በቀጣይ 6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የሚገነቡት ት/ቤቶች ቁጥር ከ1200 በላይ እንደሚሆን ሚንስትሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ቤቶቹ ዲዛይን ተሰርቶ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገለፀው በቀጣይ ከክልሎች ጋር በመሆን ኮንትራክተሮችን በመለየት ግንባታው በፍጥነት እንደሚጀመርም አብራርተዋል።
ፕሮጀክቱ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ በፍትሃዊነትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ሚንስትሩ አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተለይም ህፃናትን ከታች ጀምሮ በእውቀትና በስነ ምግባር በመቅረፅ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከ34 ሺ በላይ ትምህርቤቶችን ገንብቷል።
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀሪ ስድስት ወራት የሚከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ለክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሀላፊዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች ባገኘው ድጋፍ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙና ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው 626 ወረዳዎች ውስጥ አንድ አንድ ትምህርት ቤት የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክትም ተጠቃሚ የሚሆኑ ክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የትምህርት ሚኒስቴር ባገኘው ድጋፍ በየወረዳው በሚገነባው ትምህርት ቤት ተመሳሳይ ሌላ ት/ቤት እንዲገነቡ የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በቀጣይ 6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የሚገነቡት ት/ቤቶች ቁጥር ከ1200 በላይ እንደሚሆን ሚንስትሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ቤቶቹ ዲዛይን ተሰርቶ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገለፀው በቀጣይ ከክልሎች ጋር በመሆን ኮንትራክተሮችን በመለየት ግንባታው በፍጥነት እንደሚጀመርም አብራርተዋል።
ፕሮጀክቱ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ በፍትሃዊነትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ሚንስትሩ አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተለይም ህፃናትን ከታች ጀምሮ በእውቀትና በስነ ምግባር በመቅረፅ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከ34 ሺ በላይ ትምህርቤቶችን ገንብቷል።
Feb 09, 2026 396
የሀገር ውስጥ ዜና

መጪዎቹ ስድስት ወራት ከ1200 በላይ የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለመገንባት መታቀዱ ተገለፀ። እነዚህ ትምህርት ቤቶች እንደ ሀገር ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው ወረዳዎችን የሚገነቡ ናቸው።

የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀሪ ስድስት ወራት የሚከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ለክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሀላፊዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች ባገኘው ድጋፍ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙና ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው 626 ወረዳዎች ውስጥ አንድ አንድ ትምህርት ቤት የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክትም ተጠቃሚ የሚሆኑ ክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የትምህርት ሚኒስቴር ባገኘው ድጋፍ በየወረዳው በሚገነባው ትምህርት ቤት ተመሳሳይ ሌላ ት/ቤት እንዲገነቡ የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በቀጣይ 6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የሚገነቡት ት/ቤቶች ቁጥር ከ1200 በላይ እንደሚሆን ሚንስትሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ቤቶቹ ዲዛይን ተሰርቶ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገለፀው በቀጣይ ከክልሎች ጋር በመሆን ኮንትራክተሮችን በመለየት ግንባታው በፍጥነት እንደሚጀመርም አብራርተዋል።
ፕሮጀክቱ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ በፍትሃዊነትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ሚንስትሩ አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተለይም ህፃናትን ከታች ጀምሮ በእውቀትና በስነ ምግባር በመቅረፅ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከ34 ሺ በላይ ትምህርቤቶችን ገንብቷል።
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በቀሪ ስድስት ወራት የሚከናወኑ ተግባራትን በተመለከተ ለክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮ ሀላፊዎች ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የትምህርት ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች ባገኘው ድጋፍ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙና ምንም ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው 626 ወረዳዎች ውስጥ አንድ አንድ ትምህርት ቤት የሚገነባ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክትም ተጠቃሚ የሚሆኑ ክልሎችና የከተማ መስተዳድሮች የትምህርት ሚኒስቴር ባገኘው ድጋፍ በየወረዳው በሚገነባው ትምህርት ቤት ተመሳሳይ ሌላ ት/ቤት እንዲገነቡ የሚጠበቅባቸው በመሆኑ በቀጣይ 6 ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ አዲስ የሚገነቡት ት/ቤቶች ቁጥር ከ1200 በላይ እንደሚሆን ሚንስትሩ አብራርተዋል።
በዚህም የትምህርት ቤቶቹ ዲዛይን ተሰርቶ እየተጠናቀቀ መሆኑን ገለፀው በቀጣይ ከክልሎች ጋር በመሆን ኮንትራክተሮችን በመለየት ግንባታው በፍጥነት እንደሚጀመርም አብራርተዋል።
ፕሮጀክቱ ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በሁሉም አካባቢ በፍትሃዊነትና በጥራት ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑን ሚንስትሩ አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት መንግስት ለቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት በተለይም ህፃናትን ከታች ጀምሮ በእውቀትና በስነ ምግባር በመቅረፅ ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት በሰጠው ልዩ ትኩረት ከ34 ሺ በላይ ትምህርቤቶችን ገንብቷል።
Feb 09, 2026 322
የሀገር ውስጥ ዜና

የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል። በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ2018 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈፃፀም መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ዓመት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ እንደሚሰጥ ገልፀዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ፈተናው በወረቀትና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደረበር አንስተው በዚህ ዓመት የሚሰጠውን ማጠናቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ለዚህም የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሰራል ብለዋል።
ክልሎች በዚህ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳይኖሩ በቂ ኮምፒዩተር ፣ ኔትዎርክና አማራጭ የሀይል አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት ሰጥተው መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበው ለተማሪዎች በቂ ሥልጠና መስጠት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች ይህንን አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
እንደ ሀገር ፈተናን በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል አቅም መኖሩንና ለዚህም እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በሚመለከት በትምህርት ሚኒስቴር የዲጅታል ትምህርትና አይሲቲ ሥራ አስፈፃሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጻ አድርገዋል።
በገለፃቸውም ተማሪዎች የሚለማመዱባቸው ሞዴል ፈተናዎች በበቂ ሁኔታ የተጋጁ መሆኑን ጠቅሰው ተማሪዎች አስቀድመው እንዲለማመዱና ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስቀረት የተለያዩ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ ፈተናን ከስርቆትና ኩረጃ በፀዳ መልኩ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈፃፀም መድረክ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በዚህ ዓመት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ እንደሚሰጥ ገልፀዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ፈተናው በወረቀትና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደረበር አንስተው በዚህ ዓመት የሚሰጠውን ማጠናቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ለዚህም የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሰራል ብለዋል።
ክልሎች በዚህ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳይኖሩ በቂ ኮምፒዩተር ፣ ኔትዎርክና አማራጭ የሀይል አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት ሰጥተው መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበው ለተማሪዎች በቂ ሥልጠና መስጠት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች ይህንን አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
እንደ ሀገር ፈተናን በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል አቅም መኖሩንና ለዚህም እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በሚመለከት በትምህርት ሚኒስቴር የዲጅታል ትምህርትና አይሲቲ ሥራ አስፈፃሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ገለጻ አድርገዋል።
በገለፃቸውም ተማሪዎች የሚለማመዱባቸው ሞዴል ፈተናዎች በበቂ ሁኔታ የተጋጁ መሆኑን ጠቅሰው ተማሪዎች አስቀድመው እንዲለማመዱና ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓት ውስጥ ያጋጠሙ ስብራቶችን ለማስቀረት የተለያዩ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ ፈተናን ከስርቆትና ኩረጃ በፀዳ መልኩ ሲሰጥ መቆየቱ ይታወሳል።
Feb 09, 2026 519
የሀገር ውስጥ ዜና

አጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ የለውጥና መደበኛ ስራዎች አፈጻጸም ሂደት የተገኙ ስኬቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተጠቆመ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት የሚገመግም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የዘርፉ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በዚህም የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተጀመረበትን ግለት ጠብቆ በህብረተሰቡ ዘንድ መቀዛቀዝ እንዳይኖር እስከመጨረሻው እንዲቀጥል በቁርጠኝነት መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በተለይም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ለማስፋፋት የተሰራው ሥራ የሚደነቅ ሲሆን የበለጠ በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የአመራር አጀንዳ አድርጎ በቁርጠኝነት መፈጸም እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከዚህም ባለፈ የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥን ከመቀነስና ውጤታማነትን ከማረጋገጥ አኳያ የትምህርት ቤት ምገባን በበጀት በመደገፍ፤ ሀብት በማሰባሰብ እንዲሁም ማህበረሰቡን በስፋት በማሳተፍ ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታን መፍጠር እንደሚገባ አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ትግበራ መሠረት የመጽሐፍት አቅርቦት ላይ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ወሳኝ መሆናቸውን ያመላከቱት ሚኒስትር ዴኤታዋ አሁንም የተማሪ መፅሃፍትን አንድ ለአንድ የማድረስ ሥራ በተለይም ከቅድመ አንደኛ እስከ አንደኛ ደረጃ የክልሎችን ትኩረት የሚፈልግ በመሆኑ በፍጥነት መፈፀም ይገባል ብለዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም መገንባትና አማራጭ የመምህራን ስልጠናን እንደ አንድ የትኩረት መስክ በመያዝ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በቅድመ-አንደኛ ደረጃና በመሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርትና ክህሎትን ለማሳደግ የተጀመሩ መልካም ተሞክሮዎችን በስፋት ለማስቀጠል አመራሩ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል እየተወሠዱ ካሉ እርምጃዎች አንዱ የሆነው የማጠናከሪያ ትምህርት (Tutorial) በማጠናከር በቅርብ መከታተል እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የታቀዱ ግቦች እንዲሳኩ የተቀናጀ የአመራር ሚና እና የማህበረሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ፣ በየደረጃው የሚገኘው አካል ለተግባራዊነቱ በትጋት መስራት እንደሚገባው ክብርት ሚኒስቴር ዴኤታዋ አሳስበዋል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ባለፉት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት የሚገመግም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የዘርፉ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በዚህም የትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የተጀመረበትን ግለት ጠብቆ በህብረተሰቡ ዘንድ መቀዛቀዝ እንዳይኖር እስከመጨረሻው እንዲቀጥል በቁርጠኝነት መሠራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በተለይም የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርትን ለማስፋፋት የተሰራው ሥራ የሚደነቅ ሲሆን የበለጠ በሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ የአመራር አጀንዳ አድርጎ በቁርጠኝነት መፈጸም እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከዚህም ባለፈ የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥን ከመቀነስና ውጤታማነትን ከማረጋገጥ አኳያ የትምህርት ቤት ምገባን በበጀት በመደገፍ፤ ሀብት በማሰባሰብ እንዲሁም ማህበረሰቡን በስፋት በማሳተፍ ለተማሪዎች ምቹ ሁኔታን መፍጠር እንደሚገባ አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ትግበራ መሠረት የመጽሐፍት አቅርቦት ላይ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ወሳኝ መሆናቸውን ያመላከቱት ሚኒስትር ዴኤታዋ አሁንም የተማሪ መፅሃፍትን አንድ ለአንድ የማድረስ ሥራ በተለይም ከቅድመ አንደኛ እስከ አንደኛ ደረጃ የክልሎችን ትኩረት የሚፈልግ በመሆኑ በፍጥነት መፈፀም ይገባል ብለዋል።
ከዚህ ጎን ለጎን የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮችን አቅም መገንባትና አማራጭ የመምህራን ስልጠናን እንደ አንድ የትኩረት መስክ በመያዝ መስራት እንደሚገባ አብራርተዋል።
በቅድመ-አንደኛ ደረጃና በመሠረታዊ የጎልማሶች ትምህርትና ክህሎትን ለማሳደግ የተጀመሩ መልካም ተሞክሮዎችን በስፋት ለማስቀጠል አመራሩ በልዩ ትኩረት መስራት እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል እየተወሠዱ ካሉ እርምጃዎች አንዱ የሆነው የማጠናከሪያ ትምህርት (Tutorial) በማጠናከር በቅርብ መከታተል እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
የታቀዱ ግቦች እንዲሳኩ የተቀናጀ የአመራር ሚና እና የማህበረሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ፣ በየደረጃው የሚገኘው አካል ለተግባራዊነቱ በትጋት መስራት እንደሚገባው ክብርት ሚኒስቴር ዴኤታዋ አሳስበዋል።
Feb 08, 2026 189
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ስርዓቱን በማጎልበት ሂደት ውስጥ የቴክኖሎጂ አቅምን አጠናክሮ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ ተገለፀ።

የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ6 ወር እቅድ አፈፃፀም ምክክር የክልል ትምህርት ቢሮዎች ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄ ይገኛል።
በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችን የትምህርት ዘርፉን በሚደግፍ አግባብ እና የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በሚያሳልጥ መልኩ የተጀመሩ ስራዎችን አስፍቶ የበለጠ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትር ዴኤታዋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የትምህርት መሰረተ ልማትን ከማስፋት አንጻር በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታና ዕድሳት በስፋት መከናወኑን ጠቅሰዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተማሪዎችን ከታች ቀርጾ ለማውጣት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ ትኩረት በመስጠት በስፋት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የምገባ መርሐ ግብርን በማጎልበት የተማሪዎችን የትምህርት ቅበላ አቅም የማሳደግና ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉ መሆኑን አብራርተዋል።
የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ወደ ተግባር መግባት ለትምህርት ጥራት የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ያሉ ሲሆን የመምህራንን እጥረት ለመቀነስ እና አቅማቸውን ለመገንባት ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውንም አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ113 ሺህ በላይ ለሆኑ መምህራን የክረምት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና የተሰጠ መሆኑም ተያይዞ ተገልጿል።
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በትኩረት እየተተገበረ መሆኑንም አብራርተዋል።
የዚህ ምክክር መድረክ ዓላማም በክልሎች መካከል ተመሳሳይ አፈፃፀም እንዲኖርና የእርስ በርስ ልምድ ልውውጥና በሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ የጋራ መፍትሄ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ6 ወር እቅድ አፈፃፀም ምክክር የክልል ትምህርት ቢሮዎች ሃላፊዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት እየተካሄ ይገኛል።
በመድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ የቴክኖሎጂ አጠቃቀማችን የትምህርት ዘርፉን በሚደግፍ አግባብ እና የትምህርት ጥራትና ተደራሽነትን በሚያሳልጥ መልኩ የተጀመሩ ስራዎችን አስፍቶ የበለጠ ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚገባ አስገነዝበዋል።
ሚንስትር ዴኤታዋ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት የትምህርት መሰረተ ልማትን ከማስፋት አንጻር በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታና ዕድሳት በስፋት መከናወኑን ጠቅሰዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተማሪዎችን ከታች ቀርጾ ለማውጣት የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ ትኩረት በመስጠት በስፋት እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
የምገባ መርሐ ግብርን በማጎልበት የተማሪዎችን የትምህርት ቅበላ አቅም የማሳደግና ስራዎች ተጠናክረው የቀጠሉ መሆኑን አብራርተዋል።
የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ወደ ተግባር መግባት ለትምህርት ጥራት የተሰጠውን ትኩረት ያሳያል ያሉ ሲሆን የመምህራንን እጥረት ለመቀነስ እና አቅማቸውን ለመገንባት ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውንም አያይዘው ገልጸዋል።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ከ113 ሺህ በላይ ለሆኑ መምህራን የክረምት ልዩ የአቅም ግንባታ ስልጠና የተሰጠ መሆኑም ተያይዞ ተገልጿል።
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ልዩ የማጠናከሪያ ትምህርት ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ በሁሉም ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በትኩረት እየተተገበረ መሆኑንም አብራርተዋል።
የዚህ ምክክር መድረክ ዓላማም በክልሎች መካከል ተመሳሳይ አፈፃፀም እንዲኖርና የእርስ በርስ ልምድ ልውውጥና በሂደት ውስጥ የሚያጋጥሙ ችግሮች ላይ የጋራ መፍትሄ ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
Feb 08, 2026 308
Recent News
Follow Us