ዜና

የሀገር ውስጥ ዜና

በተለያዩ የትምህርት መስክ ሰልጥነው ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ አማራጭ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊገባ መሆኑ ተገለፀ። አዲስ በተዘጋጀው አማራጭ የመምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ላይ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስቴር በመምህርነት ሙያ የሚታየውን የሥልጠና እጥረት ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ሰልጥነው የሚገኙና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ አዲስ የአሠራር ሥርዓት ወደ ተግባር ሊያሰገባ መሆኑን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።
ሀገራችን የመምህርነት ሙያ ማሰልጠን የረጅም ጊዜ ታሪክ ያለት ቢሆንም አማራጭ ወደ መምህርነት ለመግባት ለሚፈልጉት አዲስ መንገድ መክፈት ያስፈልጋል፤ ለዚህም ተጨማሪ ሥልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሥልጠና ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ብለዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ከተደረገው የሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር አብሮ የሚሄድ ለደረጃው የሚመጥን የትምህርት ዝግጅት ያላቸው መምህራንን ለማፍራት የተለያዩ አማራጮች ተቀርፀው እየተሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በዚህም መምህር ሆነው መሥራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የሚያስተምሩት ትምህርት አይነት ይዘት ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋልም ተብሏል።
የመምህራንና የትምህር አመራር ልማት ዴስክ ሃላፊ ወ/ሮ አሰገድ ምሬሳ በበኩላቸው የሀገራችንን የመምህራን አቅርቦት ለማሻሻል አማራጭ የስልጠና ሞዳሊቲዎች እየተጠኑ ወደ ስራ ማስገባት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም በተደረገ የዳሰሳ ጥናት አብዛኞች በተለያዩ የትምህርት መስክ የተመረቁ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳለም ለማረጋገጥ ተችሏል ብለዋል።
የሥልጠና ማዕቀፉን ወደ ሥራ ለማስገባትም ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ መምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ወደ ተግባር ይገባልም ተብሏል።
Jun 05, 2025 15
የሀገር ውስጥ ዜና

ኩረጃን የሚጠየፍ ትውልድ ለመፍጠር እስካሁን በተወሰዱ እርምጃዎች በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር መቻሉ ተገለጸ።

የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የትምህርት ምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል እንደሆነ ይታወቃል።
በዚህ ሂደት እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት እውቀት ሲሆን ሰርተፊኬት ደግሞ ያንን እውቀት የምንለካበት ነው ብለዋል።
በስርቆት፣ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እውቀት ሳይኖር ሰርተፊኬት ማግኘት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ እውቀት አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተፊኬቱ እውቀት አለህ ስለሚለው ምንም ሳያቅ ሰርተፊኬት በእጁ ስላለው ብቻ እውቀት አለኝ ብሎ የሚያምን የህብረተሰብ ክፍል ይፈጠራል፤ ይህም ህብረተሰቡን በጣም እንደሚጎዳው አብራርተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ተንሰራፍቶ የነበረውን ማጭበርበር፣ ስርቆትና ኩረጃ ተማሪዎች ብቻ የሚያደርጉት ቢሆን ኖሮ የልጆቹ ችግር ነው ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። ነገር ግን ይህን የሚያደርጉት ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት አስተዳደሮች፣ የክልል ባለ ስልጠናት እና ሌሎችም የኛ አካባቢ ልጆች እንዲያልፉ በሚል የሚያደርጉት በመሆኑ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ የተገባበት እንደነበር አንስተዋል።
በመሆኑም ወደፊት ትውልዱን በጥራት ማስተማር አለብን ካልን ከመሰረቱ ችግሩን መፍታትና በኩረጃና በማጭበርበር የሚገኝ እውቀት እንደሌለና ይህም ሀገር እንደሚጎዳ በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ይህንን ስብራት ለማስተካከል በተወሰደው የለውጥ እርምጃ ተማሪዎች በትምህርት ዘርፉ በቀላሉ አጭበርብሮና ኮርጆ ማለፍ የለም የሚለውን በማወቅ በሥርዓቱ ማጥናት፣ ቤተ መጽሃፍት መግባት፣ ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም፣ በትርፍ ጊዜያቸው ቲቶሪያል መማርና ለትምህርታቸው በቂ ትኩረት መስጠት ጀምረዋል።
መምህራንም በአግባቡ ተዘጋጅተው ማስተማርና ተማሪዎችን በሚገባ ማዘጋጀት፣ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንም ሁሉም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው ከክፍል ክፍል በትክክል ተመዝነው እንዲያልፉ ማድረግ የጀመሩበት፣
በየክልሉ ያለው የትምህርት መዋቅርም በኩረጃ የኔ አካባቢ ይህን ያህል አለፈ ከሚል የቁጥር ጨዋታ ወጥተው በትክክል የትምህርት ምዘና በየደረጃው በማድረግ ልጆች ባላቸው እውቀት ብቻ ተመዝነው የሚያልፉበት ሥርዓት እየፈጠሩ ይገኛል። ለአብነትም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በአግባቡ እየተገበሩ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም ይህንን ማስቀጠል ከተቻለ የምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን በሚገባ ያስተካክለዋል። የገጠመውን የሞራል ክስረት በሚገባ አስወግዶ ትምህርት በእውቀትና በችሎታ ብቻ የሚለው በጀመርነው አግባብ ወደ ኋላ ሳይመለው ማስረጽ ከቻልን ለምናደርገው የትምህርት ጥራት መሻሻል እንደ መነሻ ይሆናልም ብለዋል።
በአጠቃላይ የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል ከተጀመረ ጀምሮ በተወሰዱ እርምጃዎች ከአሁን በኋላ በሁሉም ዘንድ ግልጽ በሆነ መንገድ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እንደሌለ እና ተምሮና ተግቶ በማጥናት ብቻ ውጤት እንደሚገኝ በተማሪዎችና በማህበረሰቡ ዘንድ መተማመን መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አክለውም ዘንድሮም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን በተለመደው አግባብ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ጠቅሰው በተለይም ከባለፈው ዓመት በተሻለ 150 ሺ የሚደርሱ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በዚህ ሂደት በቀጣይ ሶስት ዓመታት ሁሉም ተማሪዎች በበየነ መረብ የሚፈተኑበት ሁኔታ ይፈጠራል ያሉት ሚኒስትሩ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ በዚህ መልኩ መስመር ከያዘ ብቃት ያላቸውና ተወዳድሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት ሌሎች የትምህርት ጥራት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ተግባራት ላይም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በወረቀትና በበየነ መረብ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሥርዓቱ ያለውን መሰረታዊ ችግር ለመፍታት ከወሰዳቸው እርምጃዎች አንዱ የትምህርት ምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል እንደሆነ ይታወቃል።
በዚህ ሂደት እስካሁን የተሰሩ ሥራዎችን በማስመልከት ማብራሪያ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት እውቀት ሲሆን ሰርተፊኬት ደግሞ ያንን እውቀት የምንለካበት ነው ብለዋል።
በስርቆት፣ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እውቀት ሳይኖር ሰርተፊኬት ማግኘት ነው ያሉት ሚኒስትሩ ይህ ደግሞ እውቀት አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ሰርተፊኬቱ እውቀት አለህ ስለሚለው ምንም ሳያቅ ሰርተፊኬት በእጁ ስላለው ብቻ እውቀት አለኝ ብሎ የሚያምን የህብረተሰብ ክፍል ይፈጠራል፤ ይህም ህብረተሰቡን በጣም እንደሚጎዳው አብራርተዋል።
በተለይም በትምህርት ዘርፉ ተንሰራፍቶ የነበረውን ማጭበርበር፣ ስርቆትና ኩረጃ ተማሪዎች ብቻ የሚያደርጉት ቢሆን ኖሮ የልጆቹ ችግር ነው ተብሎ ሊወሰድ ይችላል። ነገር ግን ይህን የሚያደርጉት ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት አስተዳደሮች፣ የክልል ባለ ስልጠናት እና ሌሎችም የኛ አካባቢ ልጆች እንዲያልፉ በሚል የሚያደርጉት በመሆኑ ከፍተኛ የሞራል ውድቀት ውስጥ የተገባበት እንደነበር አንስተዋል።
በመሆኑም ወደፊት ትውልዱን በጥራት ማስተማር አለብን ካልን ከመሰረቱ ችግሩን መፍታትና በኩረጃና በማጭበርበር የሚገኝ እውቀት እንደሌለና ይህም ሀገር እንደሚጎዳ በሁሉም ዘንድ መተማመን መፍጠር ያስፈልጋል ብለዋል።
በዚህም ይህንን ስብራት ለማስተካከል በተወሰደው የለውጥ እርምጃ ተማሪዎች በትምህርት ዘርፉ በቀላሉ አጭበርብሮና ኮርጆ ማለፍ የለም የሚለውን በማወቅ በሥርዓቱ ማጥናት፣ ቤተ መጽሃፍት መግባት፣ ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም፣ በትርፍ ጊዜያቸው ቲቶሪያል መማርና ለትምህርታቸው በቂ ትኩረት መስጠት ጀምረዋል።
መምህራንም በአግባቡ ተዘጋጅተው ማስተማርና ተማሪዎችን በሚገባ ማዘጋጀት፣ የትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራንም ሁሉም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ተከታትለው ከክፍል ክፍል በትክክል ተመዝነው እንዲያልፉ ማድረግ የጀመሩበት፣
በየክልሉ ያለው የትምህርት መዋቅርም በኩረጃ የኔ አካባቢ ይህን ያህል አለፈ ከሚል የቁጥር ጨዋታ ወጥተው በትክክል የትምህርት ምዘና በየደረጃው በማድረግ ልጆች ባላቸው እውቀት ብቻ ተመዝነው የሚያልፉበት ሥርዓት እየፈጠሩ ይገኛል። ለአብነትም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በአግባቡ እየተገበሩ መሆኑን አንስተዋል።
በመሆኑም ይህንን ማስቀጠል ከተቻለ የምዘናና የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን በሚገባ ያስተካክለዋል። የገጠመውን የሞራል ክስረት በሚገባ አስወግዶ ትምህርት በእውቀትና በችሎታ ብቻ የሚለው በጀመርነው አግባብ ወደ ኋላ ሳይመለው ማስረጽ ከቻልን ለምናደርገው የትምህርት ጥራት መሻሻል እንደ መነሻ ይሆናልም ብለዋል።
በአጠቃላይ የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳደር ሥርዓቱን ማስተካከል ከተጀመረ ጀምሮ በተወሰዱ እርምጃዎች ከአሁን በኋላ በሁሉም ዘንድ ግልጽ በሆነ መንገድ በማጭበርበርና በኩረጃ የሚገኝ ነገር እንደሌለ እና ተምሮና ተግቶ በማጥናት ብቻ ውጤት እንደሚገኝ በተማሪዎችና በማህበረሰቡ ዘንድ መተማመን መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አክለውም ዘንድሮም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን በተለመደው አግባብ ለመስጠት በቂ ዝግጅት መደረጉ ጠቅሰው በተለይም ከባለፈው ዓመት በተሻለ 150 ሺ የሚደርሱ ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ ይወስዳሉ ብለዋል።
በዚህ ሂደት በቀጣይ ሶስት ዓመታት ሁሉም ተማሪዎች በበየነ መረብ የሚፈተኑበት ሁኔታ ይፈጠራል ያሉት ሚኒስትሩ የፈተና አስተዳደር ሥርዓቱ በዚህ መልኩ መስመር ከያዘ ብቃት ያላቸውና ተወዳድሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት ሌሎች የትምህርት ጥራት ሊያረጋግጡ የሚችሉ ተግባራት ላይም ርብርብ ይደረጋል ብለዋል።
በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች በወረቀትና በበየነ መረብ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Jun 03, 2025 347
የሀገር ውስጥ ዜና

ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር እየተሰራ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትሩ ገለፁ።

በጋምቤላ ክልል በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በጋምቤላ ክልል የሚስተዋለውን ከፍተኛ የትምህርት ጥራት ችግርና የመማሪያ ክፍል ጥበት ለመቅረፍ የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ መጀመር አስተዋጸኦ የጎላ ይሆናል ብለዋል።
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሰፊ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም በመላ ሀገሪቱ 31 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 15ቱ በትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም 16ቱ ደግሞ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት እንደሚገነቡ አንስተው በተለይም በቂ የመሰረተ ልማት ባልተሟላላቸው ክልሎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው ይህ ትምህርት ቤት በክልሉ የትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በክልላችን የተመዘገበውን ዝቅተኛ የተማሪ ውጤት ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ፈተናዎች ማለፍ የሚቻለው ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎት የተላበሱ፣ ችግር ፈቺ ፣ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስው፤
የትምህርት ጥራት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በክልሉ የትምህርት ጥራት እንዲሻሻል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የዚህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሙሉ ወጪ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፈን የተገለፀ ሲሆን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
በዚህም ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ክትትል ለማድረግ በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የሥምምነት ፊርማ ተከናውኗል።
በጋምቤላ ክልል በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት ለሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።
በማስጀመሪያ ሥነ ሥርዓቱ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በየአካባቢው መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ ተማሪዎችን ለማፍራት እየተሠራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም በጋምቤላ ክልል የሚስተዋለውን ከፍተኛ የትምህርት ጥራት ችግርና የመማሪያ ክፍል ጥበት ለመቅረፍ የዚህ ትምህርት ቤት ግንባታ መጀመር አስተዋጸኦ የጎላ ይሆናል ብለዋል።
አክለውም ሁሉም ኢትዮጵያዊ እኩል እድል አግኝቶ የሚማርበትን ምቹ ሁኔታ መፍጠር ግዴታ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ ሰፊ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በዚህም በመላ ሀገሪቱ 31 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 15ቱ በትምህርት ሚኒስቴር እንዲሁም 16ቱ ደግሞ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት እንደሚገነቡ አንስተው በተለይም በቂ የመሰረተ ልማት ባልተሟላላቸው ክልሎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል ብለዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው ይህ ትምህርት ቤት በክልሉ የትምህርት ጥራት መረጋገጥ አስተዋፅኦው የጎላ መሆኑን ጠቅሰው በክልላችን የተመዘገበውን ዝቅተኛ የተማሪ ውጤት ለማሻሻል በቁርጠኝነት እንሰራለን ብለዋል።
የ21ኛውን ክፍለ ዘመን ፈተናዎች ማለፍ የሚቻለው ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎት የተላበሱ፣ ችግር ፈቺ ፣ ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ማፍራት ሲቻል መሆኑን አንስው፤
የትምህርት ጥራት ጉዳይ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ በክልሉ የትምህርት ጥራት እንዲሻሻል ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የዚህ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ሙሉ ወጪ በሰዎች ለሰዎች ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፈን የተገለፀ ሲሆን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
በዚህም ግንባታውን በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ክትትል ለማድረግ በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የሥምምነት ፊርማ ተከናውኗል።
May 30, 2025 189
የሀገር ውስጥ ዜና

ለትምህርት ቤቶች ግንባታ መሠረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን ቀጥታ ግንባታ በማስጀመር በአጭር ጊዜ አጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምሩ የሚያስችል ስልት ተቀይሶ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስቴር በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በጋራ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት ለትምህርት ቤቶች ግንባታ የመሰረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራን በማጠናቀቅ ግንባታዎችን በማስጀመር በተግባር በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
አክለውም ይህ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም መሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን መሆኑን በመግለፅ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ብለዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ አሁን ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በፍተሃዊነትና በጥራት ለማድረስ የተጀመረው ሥራ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምቹ አካባቢን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ ትምህርት ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየሠራቸው ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በተለይም በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ እንደ ሀገር በርካታ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም በክልሉ ያለውን ክፍተት በመለየትና ልዩ ትኩረት በመስጠት ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ የሚያስገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩና የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በጋራ አስጀምረውታል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት ለትምህርት ቤቶች ግንባታ የመሰረት ድጋይ አስቀምጦ መጥፋት ሳይሆን የቅድመ ዝግጅት ሥራን በማጠናቀቅ ግንባታዎችን በማስጀመር በተግባር በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት በመዘርጋት በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
አክለውም ይህ ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ትምህርት ቤትም መሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን መሆኑን በመግለፅ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ብለዋል።
ሁሉም በሀገራችን የሚኖሩ ልጆች በተቻለ መጠን ተመጣጣኝ ትምህርት፣ እውቀትና ክህሎት ማግኘት አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ አሁን ትምህርትን ለሁሉም ዜጎች በፍተሃዊነትና በጥራት ለማድረስ የተጀመረው ሥራ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ተደራሽ ባደረገ መልኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል።
የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክብርት ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምቹ አካባቢን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን በመጥቀስ ትምህርት ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታም በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ የክልሉ መንግስት አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል ያሉ ሲሆን ህብረተሰቡም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ እኩኝ ኡኬሎ በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎች ውጤት ለማሻሻልና የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እየሠራቸው ያሉ ሥራዎች አበረታች መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
በተለይም በትምህርት ለትውልድ እንቅስቃሴ እንደ ሀገር በርካታ ትምህርት ቤቶች ቢገነቡም በክልሉ ያለውን ክፍተት በመለየትና ልዩ ትኩረት በመስጠት ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ግንባታው እስኪጠናቀቅ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ብለዋል።
May 30, 2025 175
የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካውያ ችግር በአፍሪካውያን መፍታት እንደሚገባ ተጠቆመ፤ በኢትዮጵያ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ2025 የኢራስመስ ጉባኤ ተጠናቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በጉባዔው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የአፍሪካ አገራትን ትብብር በማጠናከር የአፍሪካውያውያን ችግሮችን በአፍሪካውያን መፍታት ይገባል ብለዋል።
አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን ለመፍታት በትብብርና በቅንጅት አጽንኦት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት የሚመደበውን በጀት ከመጠቀም ባሻገር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ተልዕኳቸውን ማሳካት እንዳለባቸውና በኢራስመስ ፕሮግራምንና የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን በመጠቀም ለሀገር ልማትና ብልጽግና መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር አቶ ኮራ ጨምረው አስገንዝበዋል፡፡
በብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ ስልጠና፣ ባህልና ሳይንስ ዳይሬክተር ጄኔራል ክሌር ሄርማን የኢራስመስ ፕሮጀክት ለአፍሪካውያን እጅግ በጣም ጠቃሚ መሆኑንና አፍሪካውያን ፕሮግራሙን በአግባቡ በማስተዋወቅና በማስፋት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባዔ እጅግ በጣም ጠቃሚ እንደነበርና ብዙ ትምህርት የተገኘበት መሆኑን አንስተው በአግባቡ በመጠቀም እንደ ሀገር የተለዩ የሪፎርም ስራዎችን ማሳካት እንደሚገባና እንደ አፍሪካ በትብብር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተካሄደው በዘንድሮው የኢራስመስ 2025 ጉባኤ ከሰሃራ በታች የሚገኙ 32 የአፍሪካ አገራትን ጨምሮ ከ46 አገራት የተወከሉ ጉባኤተኞቾ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ በጉባዔው ማጠቃለያ ላይ ባስተላለፉት መልእክት የአፍሪካ አገራትን ትብብር በማጠናከር የአፍሪካውያውያን ችግሮችን በአፍሪካውያን መፍታት ይገባል ብለዋል።
አፍሪካውያን ችግሮቻቸውን ለመፍታት በትብብርና በቅንጅት አጽንኦት ሰጥተው መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል፡፡
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት የሚመደበውን በጀት ከመጠቀም ባሻገር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ተልዕኳቸውን ማሳካት እንዳለባቸውና በኢራስመስ ፕሮግራምንና የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን በመጠቀም ለሀገር ልማትና ብልጽግና መስራት እንደሚጠበቅባቸውም ክቡር አቶ ኮራ ጨምረው አስገንዝበዋል፡፡
በብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የትምህርት፣ ስልጠና፣ ባህልና ሳይንስ ዳይሬክተር ጄኔራል ክሌር ሄርማን የኢራስመስ ፕሮጀክት ለአፍሪካውያን እጅግ በጣም ጠቃሚ መሆኑንና አፍሪካውያን ፕሮግራሙን በአግባቡ በማስተዋወቅና በማስፋት መጠቀም እንዳለባቸው ጠቁመዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ጉባዔ እጅግ በጣም ጠቃሚ እንደነበርና ብዙ ትምህርት የተገኘበት መሆኑን አንስተው በአግባቡ በመጠቀም እንደ ሀገር የተለዩ የሪፎርም ስራዎችን ማሳካት እንደሚገባና እንደ አፍሪካ በትብብር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተካሄደው በዘንድሮው የኢራስመስ 2025 ጉባኤ ከሰሃራ በታች የሚገኙ 32 የአፍሪካ አገራትን ጨምሮ ከ46 አገራት የተወከሉ ጉባኤተኞቾ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
May 23, 2025 365
የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።

በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ እየተካሄደ ካለው የትምህርት ፎረሙ ጎን ለጎን ከእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮነስ ቻፕማን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም የገልጹላቸው ሲሆን በራስ አቅም በ “ትምህርት ለትውልድ’’ ህዝባዊ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻን በተመለከተ ስለተገኘው ውጤት አብራርተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ከሥርዓተ ትምህርት፣ ከመምህራንና የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና እና ከእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጋር በተያያዘ የተጀመሩ ሥራዎችን ጠቅሰው፣
እነዚህ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ሪፎርሞች በፍጥነት እንዲሳኩ የልማት አጋሮችና በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፉን እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትሯ ባሮነስ ቻፕማን በበኩላቸው በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደርጉትን ጉብኝት በማስታወስ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ለውጥ አድንቀዋል፣
የተጀመረውን የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ምንም እንኳን በእንግሊዝ መንግስት የተደረገው የበጀት ቅነሳ (budget cuts) ቢኖርም በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚካሄደውን ሪፎርም ለመደገፍ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ክቡር ሚኒስትሩ ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚንስትሮች ጋር በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በተመለከተ ውይይቶች አድርገዋል።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎርም ላይ ከ150 በላይ የትምህርት ሚኒስትሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን እየተሳተፈ እንደሚገኝም የተገለጸ ሲሆን፣
ክቡር ሚኒስትሩም በዓለም አቀፉ የትምህርት ፎረም ላይ ‘’ የገንዘብ ድጋፍን ማሻሻል፣ ውጤታማ እቅድ በማውጣትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመለየት ረገድ አንዳችን ከሌላችን ምን እንማራለን?’’ በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የመነሻ ፅሁፍ አቅርበዋል።
በትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተመራ ልኡካን ቡድን በለንደን እየተካሄደ ባለው አለም አቀፍ የትምህርት ፎረም 2025 ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ እየተካሄደ ካለው የትምህርት ፎረሙ ጎን ለጎን ከእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትር ባሮነስ ቻፕማን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።
በዚህም ክቡር ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም የገልጹላቸው ሲሆን በራስ አቅም በ “ትምህርት ለትውልድ’’ ህዝባዊ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶች መሰረተ ልማት ማሻሻን በተመለከተ ስለተገኘው ውጤት አብራርተዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ከሥርዓተ ትምህርት፣ ከመምህራንና የትምህርት ቤት ዳይሬክተሮች ስልጠና እና ከእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት ጋር በተያያዘ የተጀመሩ ሥራዎችን ጠቅሰው፣
እነዚህ በትምህርት ዘርፉ የተጀመሩ ሪፎርሞች በፍጥነት እንዲሳኩ የልማት አጋሮችና በተለይም የእንግሊዝ መንግስት ድጋፉን እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
የእንግሊዝ የአለምአቀፍ ልማት ሚኒስትሯ ባሮነስ ቻፕማን በበኩላቸው በቅርቡ በኢትዮጵያ ያደርጉትን ጉብኝት በማስታወስ በትምህርት ዘርፉ እየተደረገ ያለውን ለውጥ አድንቀዋል፣
የተጀመረውን የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ምንም እንኳን በእንግሊዝ መንግስት የተደረገው የበጀት ቅነሳ (budget cuts) ቢኖርም በኢትዮጵያ የትምህርት ዘርፍ የሚካሄደውን ሪፎርም ለመደገፍ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ክቡር ሚኒስትሩ ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚንስትሮች ጋር በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በተመለከተ ውይይቶች አድርገዋል።
በዚህ ዓለም አቀፍ የትምህርት ፎርም ላይ ከ150 በላይ የትምህርት ሚኒስትሮች የሚመራ የልዑካን ቡድን እየተሳተፈ እንደሚገኝም የተገለጸ ሲሆን፣
ክቡር ሚኒስትሩም በዓለም አቀፉ የትምህርት ፎረም ላይ ‘’ የገንዘብ ድጋፍን ማሻሻል፣ ውጤታማ እቅድ በማውጣትና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በመለየት ረገድ አንዳችን ከሌላችን ምን እንማራለን?’’ በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የመነሻ ፅሁፍ አቅርበዋል።
May 22, 2025 310
የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት ሀገራት የትምህርትና ስልጠና ተቋማት ጋር ያለውን የትብብር ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባ ተመላከተ፤ የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ (ERASMUS +) ትብብር የተዘጋጀ ጉባዔ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የትምህርትና ስልጠና አጋርነት ጥራትና ተገቢነቱን በማሳደግ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
በትምህርትና ስልጠና ተቋማት መካከል ግንኙነት በማጠናከር ውጤታማ የልማት ትብብሮችን መተግበር እንደሚገባም ወ/ሮ ሙፈሪሃት አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚና የብሔራዊ ኢራስመስ (ERASMUS +) ተወካይ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ እኤአ ከ2010 እስከ አሁን ድረስ ከ600 በላይ ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ የተጀመረው የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍና ትብብር ጉባኤ ዓላማ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገራት ያለውን የትምህርትና ስልጠና ግንኙነት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ለመምከር መሆኑንም ዶ/ር ኤባ ጨምረው ገልጸዋል።
በአውሮፓ ህብረት የትብብርና አለማቀፋዊነት ልዑክ ሃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሺሊሮ በበኩላቸው ኢራስመስ (ERASMUS) በትምህርት፣ በስልጠና ፣በወጣቶች በስፖርትና በባህል ላይ አትኩሮ የሚሰራ) የአውሮፓ ህብረት ፕሮግራም መሆኑን አስረድተዋል።
" የትምህርት ሚና በአረንጓዴ ሽግግር" በሚል ርዕስ ዛሬ የተከፈተው ይሄው ጉባኤ እስከ ረቡዕ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በጉባኤው ላይ 46 ሀገራት (13 ከአውሮፓ ህብረት ሀገራት፣ 32 ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት እና 1 ሰሜን አፍሪካ) የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በጉባኤው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የትምህርትና ስልጠና አጋርነት ጥራትና ተገቢነቱን በማሳደግ አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል።
በትምህርትና ስልጠና ተቋማት መካከል ግንኙነት በማጠናከር ውጤታማ የልማት ትብብሮችን መተግበር እንደሚገባም ወ/ሮ ሙፈሪሃት አስገንዝበዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚና የብሔራዊ ኢራስመስ (ERASMUS +) ተወካይ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) በበኩላቸው በኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍ እኤአ ከ2010 እስከ አሁን ድረስ ከ600 በላይ ኢትዮጵያውያን ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ የተጀመረው የአውሮፓ ህብረት የኢራስመስ የትምህርትና ስልጠና ድጋፍና ትብብር ጉባኤ ዓላማ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ አገራት ያለውን የትምህርትና ስልጠና ግንኙነት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ለመምከር መሆኑንም ዶ/ር ኤባ ጨምረው ገልጸዋል።
በአውሮፓ ህብረት የትብብርና አለማቀፋዊነት ልዑክ ሃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሺሊሮ በበኩላቸው ኢራስመስ (ERASMUS) በትምህርት፣ በስልጠና ፣በወጣቶች በስፖርትና በባህል ላይ አትኩሮ የሚሰራ) የአውሮፓ ህብረት ፕሮግራም መሆኑን አስረድተዋል።
" የትምህርት ሚና በአረንጓዴ ሽግግር" በሚል ርዕስ ዛሬ የተከፈተው ይሄው ጉባኤ እስከ ረቡዕ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን በጉባኤው ላይ 46 ሀገራት (13 ከአውሮፓ ህብረት ሀገራት፣ 32 ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት እና 1 ሰሜን አፍሪካ) የተወከሉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
May 20, 2025 383
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ዘርፉን አገራዊ ሪፎርም መሰረት በማድረግ ስራዎችን መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ። በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥና የሪፎርም አጀንዳዎች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

የስራ አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ይበልጣል አያሌው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የአገር አቀፍ ሪፎርም አካል የሆነው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ይገባል።
በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ለሚገባው የሪፎርም ትግበራ የመዋቅርና የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ እየተደረገ እንደሆነም ዶክተር ይበልጣል አክለው ገልጸዋል።
የአሰራር ማሻሻያውን ተከትሎም አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአዲስ መልኩ ተሻሽለው እንዲዘጋጁ መደረጉንም ተናግረዋል።
የሙከራ ትግበራው በቅድሚያ በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከዚያም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከ ትምህርት ቤቶች ደረጃ በደረጃ በተግባራዊ እንደሚደረግ አመልክተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርሞርና የማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ ዶ/ር) በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ ሪፎርሞች ተቋማቱ ተልኳቸው በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የዩኒቨርስቲዎች ዓላማ ማህበረሰብን መለወጥ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ሠራዊት ተቋማቱ ያሉባቸውን የአሰራር ተግዳሮቶች በመለየት በአፋጣኝ መፍታት እንደሚጠበቅባቸውም ጠቁመዋል።
የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ አቶ ከበደ ግዛው በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ተቋማዊ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ስራዎች የመልካም አስዳደርና የሪፎርም አጀንዳዎች የአሰራር ስርዓት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ለመገምገም መሆኑንም አቶ ከበደ ጨምረው ገልጸዋል።
የስራ አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ይበልጣል አያሌው (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት የአገር አቀፍ ሪፎርም አካል የሆነው የትምህርት ዘርፍ ሪፎርም በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ይገባል።
በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ ለሚገባው የሪፎርም ትግበራ የመዋቅርና የአሰራር ስርዓት ማሻሻያ እየተደረገ እንደሆነም ዶክተር ይበልጣል አክለው ገልጸዋል።
የአሰራር ማሻሻያውን ተከትሎም አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች በአዲስ መልኩ ተሻሽለው እንዲዘጋጁ መደረጉንም ተናግረዋል።
የሙከራ ትግበራው በቅድሚያ በትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ከዚያም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እስከ ትምህርት ቤቶች ደረጃ በደረጃ በተግባራዊ እንደሚደረግ አመልክተዋል።
በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርሞርና የማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ ዶ/ር) በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ ሪፎርሞች ተቋማቱ ተልኳቸው በአግባቡ እንዲወጡ እንደሚያስችል ተናግረዋል።
የዩኒቨርስቲዎች ዓላማ ማህበረሰብን መለወጥ መሆኑን የጠቆሙት ዶክተር ሠራዊት ተቋማቱ ያሉባቸውን የአሰራር ተግዳሮቶች በመለየት በአፋጣኝ መፍታት እንደሚጠበቅባቸውም ጠቁመዋል።
የተቋማዊ ለውጥ ስራ አስፈጻሚ አቶ ከበደ ግዛው በበኩላቸው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄዱ የሪፎርም አጀንዳዎች ተቋማዊ ሊሆኑ እንደሚገባ አስረድተዋል።
የውይይት መድረኩ ዓላማ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የለውጥ ስራዎች የመልካም አስዳደርና የሪፎርም አጀንዳዎች የአሰራር ስርዓት ማስፈጸሚያ ስትራቴጂ ለመገምገም መሆኑንም አቶ ከበደ ጨምረው ገልጸዋል።
May 19, 2025 302
የሀገር ውስጥ ዜና

የትምህርት ሚኒስትሩ በአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሜንያ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እና አርሜንያ ግንኙነት ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑን በማንሳት በትምህርት ዘርፉ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ጥልቅ ሪፎርም በማካሄድ የትምህርት ሥርዓቱን በመቀየር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ፣ ክህሎት ያላቸው፣ ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት በርካታ ሥራዎችን እየሰራች እንደምትገኝ ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ሥርዓቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ ለማላቀቅ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ረገድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር በቀጣይ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችንም ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በትምህርት ዘርፉ እየተወሰዱ ባሉ ሪፎርሞች ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውንም ለቡድን አባላቱ አብራርተዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር አርቱር ማርቲሮስያን በበኩላቸው አርሜንያና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው አንስተው ይህንን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ እንፈልጋለን ብለዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ በከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲ ግንኙነት፣ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጅነሪግና ሂሳብ (STEM)፣ በጤና ትምህርት ፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ለአርሜንያ ስትራቴጂክ በመሆኗ ለምስራቅ አፍሪካ የትብብር ማዕከል ማድረግ እንፈልጋለን ያሉት ምክትል ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሁለቱ አካላት በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራንና አካዳሚክ ልውውጥ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ረገድ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም ሰፊ ውይይቶችን አድርገዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአርሜንያ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር የተመራ ልዑካን ቡድንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ እና አርሜንያ ግንኙነት ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑን በማንሳት በትምህርት ዘርፉ ያላቸውን ትብብር የበለጠ ማጠናከር ይገባቸዋል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ጥልቅ ሪፎርም በማካሄድ የትምህርት ሥርዓቱን በመቀየር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ፣ ክህሎት ያላቸው፣ ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት በርካታ ሥራዎችን እየሰራች እንደምትገኝ ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገልጸዋል።
በተለይም የትምህርት ሥርዓቱን ከፖለቲካ ተጽዕኖ ለማላቀቅ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ጠቅሰው ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ረገድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር በቀጣይ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችንም ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
በዚህም በትምህርት ዘርፉ እየተወሰዱ ባሉ ሪፎርሞች ከሀገራት ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውንም ለቡድን አባላቱ አብራርተዋል።
የአርሜንያ ሪፐብሊክ የትምህርት፣ የሳይንስ፣ የባህልና ስፖርት ምክትል ሚኒስትር አርቱር ማርቲሮስያን በበኩላቸው አርሜንያና ኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው አንስተው ይህንን ወደ ላቀ ደረጃ ማሳደግ እንፈልጋለን ብለዋል።
አክለውም በትምህርቱ ዘርፍ በከፍተኛ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲ ግንኙነት፣ በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጅነሪግና ሂሳብ (STEM)፣ በጤና ትምህርት ፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በቴክኖሎጂ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ዘርፍ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ትልቅ ሀገርና ለአርሜንያ ስትራቴጂክ በመሆኗ ለምስራቅ አፍሪካ የትብብር ማዕከል ማድረግ እንፈልጋለን ያሉት ምክትል ሚኒስትሩ በዚህ ረገድ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በተጨማሪም ሁለቱ አካላት በተማሪዎች ነጻ የትምህርት እድል፣ በምሁራንና አካዳሚክ ልውውጥ እንዲሁም በጥናትና ምርምር ረገድ በትብብር መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም ሰፊ ውይይቶችን አድርገዋል።
May 14, 2025 263
የሀገር ውስጥ ዜና

የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

ትምህርት ሚኒስቴር ለማስገንባት ካቀዳቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በዛሬው እለት ተጀምሯል።
ይህ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ የሚገነባውን ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አስጀምረውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ ሞዴል ትምህርት ቤት አርብቶ አደር በሆነ አካባቢ የሚገነባ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ለሁሉም ዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማዳረስ የምናደርገውን ጥረት ያሳያል ብለዋል።
እንደ ሀገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ በአለም ላይ ተወዳዳሪ የሆኑ፤ ብቃትና ክህሎት ያላቸው የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት እንደዚህ ያሉ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች ያስፈልጋሉ፤ ለዚህም አቅደን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ከኛ የተሻለ ማሰብ የሚችሉ፣ ሀገር የሚመሩ ተተኪ ትውልዶች ከመንደርና አካባቢ ወጥተው ስለ ሀገር ማሰብ የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የበለጠ መረባረብ አለብን ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 500 ሚሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል።
ትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ተጠይቋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ለማስገንባት ካቀዳቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የያቤሎ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በዛሬው እለት ተጀምሯል።
ይህ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ያቤሎ ከተማ የሚገነባውን ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አስጀምረውታል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ይህ ሞዴል ትምህርት ቤት አርብቶ አደር በሆነ አካባቢ የሚገነባ መሆኑን ጠቅሰው ይህ ለሁሉም ዜጎች ጥራት ያለው ትምህርትን በፍትሃዊነት ለማዳረስ የምናደርገውን ጥረት ያሳያል ብለዋል።
እንደ ሀገር ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥኑ በአለም ላይ ተወዳዳሪ የሆኑ፤ ብቃትና ክህሎት ያላቸው የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት እንደዚህ ያሉ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች ያስፈልጋሉ፤ ለዚህም አቅደን እየሰራን እንገኛለን ብለዋል።
ከኛ የተሻለ ማሰብ የሚችሉ፣ ሀገር የሚመሩ ተተኪ ትውልዶች ከመንደርና አካባቢ ወጥተው ስለ ሀገር ማሰብ የሚችሉ ዜጎችን ለማፍራት የበለጠ መረባረብ አለብን ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በትምህርት ሚኒስቴር የሚሸፈን ሲሆን 500 ሚሊየን ብር ይፈጃል ተብሏል።
ትምህርት ቤቱ ግንባታም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ እንደሚጀምር የተገለፀ ሲሆን ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግም ተጠይቋል።
May 03, 2025 262
የሀገር ውስጥ ዜና

በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያይተዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ሰው እውቀትና እውነት ፈልጎ የሚመጣባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጥሮ የተሰጡ የአካባቢው ፀጋዎች ላይ ራዕይ ይዘው መሥራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲም በማዕድን ላይ ሰፊ ምርምር በማድረግ ህብረተሰቡን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ሥራ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግን ዋና ተግባራቸው አድርገው መሥራት አለባቸው፦
በዚህ ረገድ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች ካስመዘገቡ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።
የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የተልዕኮ መስክ ልየታ መሠረት ትኩረት አድርገው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የሥነ ምግባር ፋና በመሆናቸው ተማሪዎቻቸውን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በጥንካሬና በክፍት የተለዩትን ጉዳዮች ያቀረቡት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት የአሰተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ።
ዩኒቨርስቲው ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን በማፍራት ተመራጭ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ራዕይ ይዞ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቡሉሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ረገድ አሉ ያላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎች ሰው እውቀትና እውነት ፈልጎ የሚመጣባቸው ተቋማት ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች በተፈጥሮ የተሰጡ የአካባቢው ፀጋዎች ላይ ራዕይ ይዘው መሥራት ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲም በማዕድን ላይ ሰፊ ምርምር በማድረግ ህብረተሰቡን ብሎም ሀገርን የሚጠቅም ሥራ መስራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሯቸው ተማሪዎች ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ማድረግን ዋና ተግባራቸው አድርገው መሥራት አለባቸው፦
በዚህ ረገድ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች በመውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች ካስመዘገቡ በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።
የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች በተሰጣቸው የተልዕኮ መስክ ልየታ መሠረት ትኩረት አድርገው ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
አክለውም ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የሥነ ምግባር ፋና በመሆናቸው ተማሪዎቻቸውን ማብቃት ላይ ትኩረት አድርገው ሊሰሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በጥንካሬና በክፍት የተለዩትን ጉዳዮች ያቀረቡት ደግሞ የከፍተኛ ትምህርት የአሰተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ሲሆኑ።
ዩኒቨርስቲው ብቃት ያላቸውና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን በማፍራት ተመራጭ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ራዕይ ይዞ መሥራት ይጠበቅበታል ብለዋል።
የቡሉሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላትም በአካዳሚክ እና በአስተዳደር ረገድ አሉ ያላቸውን ጥያቄዎች አንስተው ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
May 03, 2025 235
የሀገር ውስጥ ዜና

ትምህርት ሚኒስቴር ከሚያስገነባቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ አንዱ የሆነው የአጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የሚያስገነባው አጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
ግንባታውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።
ትምህርት ዓለም ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ በመሆኑ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት ከመሠረቱ በመቀየር ሀገር የሚገነባ ቀጣይ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ይህ በሻኪሶ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ያለውን የትምህርት ቤት እጥረት የሚፈታ ይሆናል።
በዚህም የከተማው አስተዳደርና አባገዳዎች ትምህርት ሚኒስቴር ያለውን ችግር በመመልከት ይህንን ትምህርት ቤት ግንባታ በሻኪሶ በማስጀመሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ከአስር እስከ አሥራ ሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ከሚያስገነባቸው ት/ቤቶች በተጨማሪም የ”ትምህርት ለትውልድ'' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት እንዲደረግላቸው ማድረጉም በመድረኩ ተገልጿል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልል ቡኡራ ቦሩ፣ ኢፋ ቦሩ እንዲሁም አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት እና ህብረተሠቡን በማስተባበር በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውም ተብራርቷል።
በተለይም የትምህርት ጥራት ችግርን ከመሠረቱ ለማስተካከል ከ17ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ከሁለት ሚሊየን በላይ ህፃናት እንዲማሩ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን።
ክልሉ በትምህርቱ ዘርፍ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና በሳይንስና ቴክኖሎጂ የዳበሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑም ተጠቅሷል።
በክልሉ በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመሩት ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በቂ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
ሚኒስቴሩ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ሻኪሶ ከተማ የሚያስገነባው አጋ ጢንጠኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀምሯል።
ግንባታውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዚዳንት ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) አስጀምረውታል።
ትምህርት ዓለም ላይ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ በመሆኑ የሀገራችንን የትምህርት ሥርዓት ከመሠረቱ በመቀየር ሀገር የሚገነባ ቀጣይ ትውልድ ለማፍራት በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
ይህ በሻኪሶ ከተማ የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በከተማው ያለውን የትምህርት ቤት እጥረት የሚፈታ ይሆናል።
በዚህም የከተማው አስተዳደርና አባገዳዎች ትምህርት ሚኒስቴር ያለውን ችግር በመመልከት ይህንን ትምህርት ቤት ግንባታ በሻኪሶ በማስጀመሩ ምስጋና አቅርበዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ከአስር እስከ አሥራ ሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃልም ተብሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር በራሱ ከሚያስገነባቸው ት/ቤቶች በተጨማሪም የ”ትምህርት ለትውልድ'' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ በመላ ሀገሪቱ በማስጀመር ከ80 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እንዲሁም የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት እንዲደረግላቸው ማድረጉም በመድረኩ ተገልጿል።
በዚህም የኦሮሚያ ክልል ቡኡራ ቦሩ፣ ኢፋ ቦሩ እንዲሁም አዳሪ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት እና ህብረተሠቡን በማስተባበር በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውም ተብራርቷል።
በተለይም የትምህርት ጥራት ችግርን ከመሠረቱ ለማስተካከል ከ17ሺ በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ከሁለት ሚሊየን በላይ ህፃናት እንዲማሩ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን።
ክልሉ በትምህርቱ ዘርፍ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥና በሳይንስና ቴክኖሎጂ የዳበሩ የነገ ሀገር ተረካቢ ዜጎችን ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑም ተጠቅሷል።
በክልሉ በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተጀመሩት ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ ጥራታቸውን ጠብቀው በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በቂ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
May 02, 2025 233
የሀገር ውስጥ ዜና

ሁለም ዜጎች እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ እየተሠራ መሆኑ ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ከተማ የኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።

በዚሁ ጊዜ የመሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቾን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየገነባ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ በትኩረት እየተሠራ ነው ያሉ ሲሆን፦
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገሪቱ ከሌላው አለም ጋር ተወዳዳሪ እንድትሆን፤ ብቁ ተወዳዳሪ፣ ክህሎትን የተላበሱና ግብረ ገብነት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ በበኩላቸው ትምህርት ሚነስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየሠራ ያለው ሥራ የሚመሰገን መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ትምህርትን ከመሠረቱ ለመቀየር ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ድረስ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ትምህርት ቤቶችን መገንባት መቻሉን ጠቅሰዋል።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ አካባቢ በርካታ ተማሪዎች ያሉበት በመሆኑ አሁን የሚገነባው ትምህርት ቤት የተማሪ ጥምርታን በማስተካከል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
በተለይም ግንባታው እንዲጀመር ቦታ በመዘጋጀትና ካሳ በመክፈል የከተማ አስተዳደሩ ለሠራው ሥራ አመስግነው የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ስታታንዳርዱን ጠብቆ በአስር ወር ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ለዚህም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የስምምነት ፊርማ ተፈርሟል።
በዚሁ ጊዜ የመሠረተ ልማት የተሟላላቸው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶቾን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየገነባ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ ግንባታው የተጀመረው ኡታ ዋዩ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እኩል የትምህርት እድል እንዲያገኙ በትኩረት እየተሠራ ነው ያሉ ሲሆን፦
ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር በርካታ የሪፎርም ተግባራትን ቀርፆ እየተገበረ ይገኛል ብለዋል።
ሀገሪቱ ከሌላው አለም ጋር ተወዳዳሪ እንድትሆን፤ ብቁ ተወዳዳሪ፣ ክህሎትን የተላበሱና ግብረ ገብነት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችሉ ሥራዎችም እየተሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።
በግንባታ ማስጀመሪያው ላይ የተገኙት በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ሳዳት ነሻ በበኩላቸው ትምህርት ሚነስቴር የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየሠራ ያለው ሥራ የሚመሰገን መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ ትምህርትን ከመሠረቱ ለመቀየር ከቅድመ መደበኛ ጀምሮ እስከ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ድረስ ህብረተሰቡን በማሳተፍ በርካታ ትምህርት ቤቶችን መገንባት መቻሉን ጠቅሰዋል።
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ(ዶ/ር) በበኩላቸው ይህ አካባቢ በርካታ ተማሪዎች ያሉበት በመሆኑ አሁን የሚገነባው ትምህርት ቤት የተማሪ ጥምርታን በማስተካከል ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
በተለይም ግንባታው እንዲጀመር ቦታ በመዘጋጀትና ካሳ በመክፈል የከተማ አስተዳደሩ ለሠራው ሥራ አመስግነው የትምህርት ቤቱ ግንባታ እስኪጠናቀቅም አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ቤቱ ግንባታ ስታታንዳርዱን ጠብቆ በአስር ወር ይጠናቀቃል የተባለ ሲሆን ለዚህም በትምህርት ሚኒስቴርና በክልሉ ትምህርት ቢሮ መካከል የስምምነት ፊርማ ተፈርሟል።
May 01, 2025 213
የሀገር ውስጥ ዜና

ትምህርት ሚኒስቴር በአለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባው ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ተጀመረ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባውን ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ያለው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንድ ብቻ በመሆኑ ይህ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያለውን ችግር በመፍታትና የተማሪ ክፍል ጥምርታውን በማመጣጠን ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ።
ምቹና መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች መኖር ምቹ መማር ማስተማርን ከመፍጠር ባሻገር ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቹን ወደው እንዲመጡም ያደርጋል ተብሏል።
በመድረኩም በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የትምህርት ጥራትን ከመሠረቱ ለመፍታት በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ስታንዳርዳቸውን የጠበቁ 21 የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመራቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ከ86 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት መደረጉ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ትምህርትን በባለቤትነት ለመደገፍ የሚያደረገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።
የተጀመረው የትምህርት ቤት ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀምር ሲሆን ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ኃላፊነቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲወጣ የስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቂ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ በተመረጡ አካባቢዎች ለመገንባት አቅዶ እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ትምህርት ሚኒስቴር በሲዳማ ክልል ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አለታ ጩኮ ከተማ የሚያስገነባውን ሩፎ ዋኤኖ ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታን አስጀምረዋል።
በከተማ አስተዳደሩ ያለው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንድ ብቻ በመሆኑ ይህ በትምህርት ሚኒስቴር የሚገነባው ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያለውን ችግር በመፍታትና የተማሪ ክፍል ጥምርታውን በማመጣጠን ለትምህርት ጥራት መረጋገጥ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል ።
ምቹና መሠረተ ልማት የተሟላላቸው ትምህርት ቤቶች መኖር ምቹ መማር ማስተማርን ከመፍጠር ባሻገር ተማሪዎች ትምህርት ቤቶቹን ወደው እንዲመጡም ያደርጋል ተብሏል።
በመድረኩም በደቡባዊ ሲዳማ ዞን የትምህርት ጥራትን ከመሠረቱ ለመፍታት በትምህርት ለትውልድ የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል ህዝባዊ ንቅናቄ ስታንዳርዳቸውን የጠበቁ 21 የሚሆኑ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተገንብተው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመራቸው ተገልጿል።
በተጨማሪም ከ86 ሚሊየን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የነባር ትምህርት ቤቶች ጥገናና እድሳት መደረጉ የተገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ትምህርትን በባለቤትነት ለመደገፍ የሚያደረገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።
የተጀመረው የትምህርት ቤት ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ የመማር ማስተማር ሥራ የሚጀምር ሲሆን ግንባታው ጥራቱን ጠብቆ እንዲጠናቀቅ በማድረግ በኩል ኃላፊነቱን የክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲወጣ የስምምነት ፊርማ ተፈራርመዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቂ መሠረተ ልማት የተሟላላቸው 50 ሞዴል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በመላ ሀገሪቱ በተመረጡ አካባቢዎች ለመገንባት አቅዶ እየሠራ እንዳለ ይታወቃል።
May 01, 2025 230
Recent News
Follow Us